Quantcast
Channel: Bawza
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1835

የፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ “ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳዊያን እና የኢትዮጵያዊያን ታሪክ”የመፅሀፍ ምርቃት ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ..

$
0
0

ጥቅምት 28/2010ዓም በቤሔራዊ ቲያትር በተመረቀው የፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ “ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳዊያን እና የኢትዮጵያዊያን ታሪክ” የመፅሀፍ ምርቃት ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የክብር እንግዳ ሆኖ ሲገኝ በአዳራሹ የነበረው ህዝብ ለተመስገን ያሳየው አክብሮት እጅጉን ደስ የሚያሰኝ ነበር።
መድረኩን የሚመራው ጋዜጠኛ በፍቃዱ አባይ ይህን ብሏል “በማይናወጥ አቋሙ የሚታወቀው የሁላችንም አንደበት የሆነው በሀገር ውስጥ ከሀገር ወጪ ተቀባይነት ያለው ባለ ብዙው ተከታዩ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በመሀከላችን ይገኛል” ሲል ህዝቡ ከመቀመጫው በመነሳት ለተመስገን ያሳይው ፍቅር ደስ የሚያሰኝ ነበር። በፍቃዱም ንግግሩን ቀጥሎ “ተሜ ለከፈልከው አንዱ ትልቁ ዋጋ እናመሰግናለን” ብሏል ህዝቡም ከተሜ ጋር መሆኑን አሳይቷል።
ተመስገን በወግብና በጀርባ ህመሙ ምክኒያት ብዙ መቀመጥ ሳይችል መፅሀፉን መርቆ ዝግጅቱ ሳያልቅ ለመውጣት ተገዷል።
የመፅሀፍ ምርቃት አዘጋጆችን እና በሔራዊ ቲያትር ቤት የነበሩትን ህዝቦች እጅጉን እናመሰግናለን።
(ቪዲዩን ተመልከቱት)
Tariku Desalegn

Posted by Tariku Desalegn on Friday, November 10, 2017

The post የፕሮፌሰር ፍቅሬ ቶሎሳ “ስውሩና ያልተነገረው የአይሁዳዊያን እና የኢትዮጵያዊያን ታሪክ” የመፅሀፍ ምርቃት ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ.. appeared first on Bawza NewsPaper.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1835

Trending Articles