Quantcast
Channel: Bawza
Viewing all articles
Browse latest Browse all 1835

በዚህ ፎቶ ላይ የሚታዩት እነ ማን ናቸው? በስንት አመት ምህረት ነው ፎቶውን የተነሱት?

$
0
0

በዚህ ፎቶ ላይ የሚታዩት እነ ማን ናቸው? በስንት አመት ምህረት ነው ፎቶውን የተነሱት? እንዚሀ ሰዎች በጋራ አንድ ጉልህ ስህተት ፈጽመው ነበር:: ምን ነበር ያ ስህተት? በፎቶው ላይ ሁሉም አንድ የጋራ መጠሪያ ተሰቷቸው ነበር:: ይህ መጠሪያ ምን ይባላል? እጃቸውን ያነሱት ማንና ማን ናቸው? የእጃቸው አነሳሰ ላይ ምን ልዩ ነገር ይስተዋላል? መልሱ እንደሚከተለው ነው:

1.በፎቶውላይ ከፊትለፊት የሚታዩ ት ከግራ ወደ ቀኝ: የብሄራዊ አትሌቲክስ አሰልጣኝ ንጉሴ ሮባ : አትሌት ብርሃኑ ግርማ : ምሩጽ ይፍጠር: ደረጀ ነዲና መሃመድ ከድር:: ከኋላ የሚታዩት ከግራ ወደ ቀኝ: አትሌት እሸቱ ቱራ : ግርማ ወልደሃና : ቶሎሳ ቆቱ: ከበደ ባልቻ ( ተሸፍኗል)::
2: ፎቶውን የተነሱት ስፔን ሀገር የተደረገው የ1973ቱን አ.ም. ( በአውሮፓ አቆጣጠር 1981) የአለም ሃገር አቋራጭ 12 ኪሜ ውድድር ላይ ለመካፈል በሚጓዙበት ወቅት ነው::
3: የፈጸሙት ስህተት: ውድድሩን ሁሉም አንድ ላይ ሆ ነው እየመሩ ሳለ ገና ለመጨረስ 2 ዙር እየቀራቸው አንድ ዙር ብቻ የቀራቸው መስሏዋቸው በከፈተኛ ፍጥነት ሮጠው ውድድሩ ሳያልቅ መቆማቸው ነው:: ከመካከላቸው መሃመድ ከድር እንደምንም የቀረውን ዙር በስሀተታቸው ተጠቃሚ የሆ ነውን አሜሪካዊ ሯጭ (ክሬግ) ተከትሎ 2 ኛ ወጣ:: ሌሎቹ ለመጨረስ ያህል ብቻ ሮጠው ግርማ ብርሃኑ 7 ኛ: ደረጀ ነዲ13 ኛ: ከበደ ባልቻ 14 ኛ : ምሩጽ ይፍጠር 15 ኛ እሸቱ ቱራ 30ኛ : ግርማ ወልደሃና 32ኛ ቶሎሳ ቆቱ 75ኛ ሆነው ጨረሱ:፡ይህ ውጤት ደረጃቸውን አይወክልም:: በ 1979 የአለም 10000 ሜተር ሻምፒዮና ምሩጽ ክሬግን እጅግ አዋርዶት ነው ያሸነፈው ( Yifter blew craig away፣said the commentator)::
4: የጋራ መጠሪያቸው አርንጓዴው ጎርፍ ( Green flood) ይህም የሆ ነው በዚህ ውድድር ላይ ሁሉም አትሌቶች አርንጓዴ ቀለም ያለው መለያ ለብሰው ውድድሩን በከፍተኛ ፍጥነት እጅብ ብለው በጋራ በመሮ ጣቸው ነው::
5: እጃቸውን ወደ ላይ ያነሱት አትሌቶች ብርሃኑ ግርማ እና ምሩጽ ይፍጠር ናቸው:: እጃቸውን በመጨበጥ ወደ ላይ ያነሱበት ፋሽን በአጠቃላይ የተጨቆኑ ወዛደሮች የትብብርና አንድነት መፈክር ፋሽን ሲሆን ሁለቱም አትሌቶች ግራ እጃቸውን ነው ያነሱት: ይህ ደግሞ የወቅቱን ኢትዮጵያን ጨምሮ የኮምኒስትን ርእዮተ አለምን በሚከተሉ ሀገሮች የተለመደ ፋሽን ነበር::

Source: Ababu Teklemariam Tiruneh face book page

The post በዚህ ፎቶ ላይ የሚታዩት እነ ማን ናቸው? በስንት አመት ምህረት ነው ፎቶውን የተነሱት? appeared first on Bawza NewsPaper.


Viewing all articles
Browse latest Browse all 1835

Trending Articles