የኢትዮጵያ የእግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የኮትዲቯር አቻውን አሸነፈ፡፡
ጨዋታው በኢትዮጵያ 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡

ሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ለአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታቸውን በባሕር ዳር ዓለምአቀፍ ስታዲዬም ዛሬ ሕዳር 9/2012 ዓ.ም አካሂደዋል፡፡
በጨዋታውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የኮትዲቯር አቻውን አሸንፏል፡፡
ሽመልስ በቀለ እና ሱራፌል ዳኛቸው ናቸው ለኢትዮጵያ ግቦችን ያስቆጠሩት፡፡
Source: Amhara Mass Media Agency